መዝሙር 23 – የዳዊት የመጽናናት፣ የሰላም እና የመታመን ጸሎት “በሞት ጥላ ሸለቆ ውስጥ እንኳን ብሄድ፣ አንተ ከእኔ ጋር ስለሆንክ ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኩዝህ ያጽናኑኛል። በጠላቶቼ ፊት ገበታ ታዘጋጅልኛለህ፤ ራሴን በዘይት ቀባኸው፤ ጽዋዬም ሞልቶ ይፈሳል። ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፤ እኔም በእግዚአብሔር ቤት ለዘላለም እኖራለሁ።” (ቁጥር 4–6) መዝሙር 23 በብዙ አማኞች የሚወደድና የሚታመን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ነው። ይህን መዝሙር በጸሎት ስታነብና በቃሉ ላይ ስታሰላስል፣ ልብህን ያጽናናል፣ በመልካሙ እረኛችን ላይም እምነትና መተማመን ያሳድራል። መዝሙር 23ን ለጸሎት ሕይወትህ እንዲረዳህ ደጋግመን ብናነብ ፤ እንዲሁም የእግዚአብሔርን መጽናናት ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች ለማካፈል ትጠቀምበታለህ።
https://t.me/Gaaela_Gaarii/2047